የእዚህ ድረገጽ አላማ እንዲሆን የምንመኘው ወንጌል ለሁሉ እንዲዳረስ አንድ ተጨማሪ ድረገጽ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ (website) ማበርከት ነው ፣ በግልም ይሁን ከተለያየ ቦታ ጀማሪ ከሆኑ ክርስቲያኖች የሚቀርቡልንን መንፈሳዊ ጥያቄዎች ከመምህራን ጋር በመሆን በማጣቀሻ የተደገፈ መልስ እንዲያገኙ መርዳት ነው።

በዚህ ድረገጽ ላይ ያካፈልናቸው ድምጾችም ሆኑ መጣጥፎች ለጊዜው ከድምጹ ባለቤቶችም ሆነ ድምጹን ከቀረጹት ባለሞያዎች የተገኘ ምንም አይነት ፈቃድ የለንም። ወደፊት በዚህ ገጽ ለማጋራት ላሰብናቸው መጣጥፎችም እንዲሁ።  ምንም አይነት ንግድና ከትርፍ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በዚህ ገጽ ላይ የማካፈል እቅድ ስለሌለን አላማው ከጅምሩ ግልጽ እንዲሆን እንፈለጋለን። ስለዚህ ድረገጽ አጀማመር ለማወቅ ይህን ይጫኑ። 

ያጋራናቸው ስብከቶችና መጣጥፎች በተፈለገ ጊዜ በቀላሉ ይገኝ ዘንድ በመልክ መልኩ አስቀምጠናል። የረቀቁ ፍለጋዎችን ( advanced search ) መጠቀምም ይቻላል። ተመዝግበን የተለያዩ ስብከቶችን እና መጣትፎችን ማጋራት፤ ጥያቄዎችን መጠየቅና ልምድ ማካፈል ያስችለናል። በተለይም በገነት ጽጌ ሰንበት ትምህርት ቤት ያለፋችሁ እግዚአብሔር ጸጋውን ያበዛላቹ ወንድሞችና እህቶች የምትጽፏቸውን መጣጥፎች በዚህ ድረገጽ በማጋራት ተደራሽነታቸውን በማሳደግ ለብዙዎች ህይወት እንዲሆኑ ማድረግ ትችላላችሁ።  እንዳስፈላጊነቱ፣ ለአባላት ብቻ የሚጋሩ ( only registerd memebers)  የተለያዩ ክፍሎችን በመጨመር ልንጠቀም እንችላለን። ለጊዜው ፤ የተመልካች ቁጥሩ 1000 እስኪደርስ አስተያየት ለመሰብሰብ እንዲረዳን ሁሉንም ገጾችህ ከፍት አድርገናቸዋል (  except for the online learning section )

ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን፤

 

ስብከቶች (Preaching)

  • 6585

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 5208

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 5303

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል...

    Read more: አብርሃም

  • 5193

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 4325

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form