አቤላክ ባኮስ,
ተወዳጆች እንደምን አላችሁ?
አንድ በኅብረት ማየት ያለብን ነገር ማቅረብ ፈልጌ ነው አንዳንድ አሳብ እንድታጋሩ ተዘጋጁ፡፡
 ወለህ ነቅዐ ሕይወት  ጉባኤ ቤት ከተመሠረተበት ዕለትና ሰዓት ጀምሮ አከባቢያዊ ፈተና ቢጋረጥበትም የተመሠረተበትን ዓላማ ለማሳካት ሐዋርያዊ እንቅስቃሴውን በከተማም ሆነ በገጠር እያፋጠነ ይገኛል፡፡
 ለዚህም ብዙ የአገልግሎቱ ደጋፊ ምእመናን ያሉት መሆን እየቻለ ነው፡፡


ነገር ግን አሁን ያለው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በከተማም ይሁን በገጠር ለአማኞቹ በሚገባቸው መልኩ ሳይሆን ደስ እንዳለን የፈለግነውን ሁሉ እየጫኑ መመለስ እየሆነ ስለሆነ ምእመናንን ባሳተፈ በአዲስ መልክ ለምእመናን በሚመጥን መልኩ ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቶ ለሰው ሕይወትም እውቀትም መሆን በሚያስችል መንገድ ቀርጾ የአማናዊት ሃይማኖታችን መመርያዎች የሆኑ ሦስቱን ምስጢራት ለይቶ እያስተማረ ይገኛል፡፡እኒህም፡-
1.ዶግማ 
2.ሥርዓት 
3.ትውፊት ናቸው
1.ዶግማ ማለት በዘመንና በጊዜ መቀየር ይቀየራል ተብሎ የማይታሰብ በሰው አእምሮ መጠን ይመጠን ተብሎም መቅለል የማይችል የማይቀየር እና  የማይሻሻል የማይለወጥ ፅኑዕ መሠረተ እምነት ማለት ነው፡፡
ይህም:-
-ስለነገረ እግዚአብሔር ያለውን ትምህርት አንድነቱንና ሦስትነቱን 
-ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ከሦስትነቱ ከአንድነቱ ሰይወጣ ከድንግል ማርያም ሰው መሆኑን
-ስለ ድንግል ማርያም ድንግልና እና ወላዲተ አምላክነት እንዲሁም  አማላጅነት
-አንዲት ስለሆነችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ቅድስት መሆን ኩላዊነትና ሐዋርያዊነት 
-ስለመላእክት ተራዳኢነት እና ተልእኮ
-ስለ ቅዱሳን ተጋድሎና ቅድስና እንዲሁም አማላጅነት እና ቃል ኪዳን 
-ስለመጽሐፍ ቅዱስ እውነተኛነት እና ቅዱስነት ሌላውንም ያካተተ ነው፡፡
2.ሥርዓት 
ሥርዓት ማለት መለኪያ ደንብ አጥር ማለት ነው ቤተ ክርስቲያን ያለ ሥርዓት መኖር አትችልም
ሁሉን በሥርዓት አድርጉ እንዳለ ሐዋርያው
ይህም 
-ስለ ማኀሌቱ ኪዳኑ ቅዳሴው 
-ስለመግባት መውጣት 
-በውስጥ ስለሚፈጸመው አገልግሎት ሁሉ 
-እንዲሁም ምእመናን በቤታቸው በሥራ ቦታቸው የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴያቸው ሁሉ ሊኖሩት ስለሚገባው ሥርዓት እና ደንብ 
-ስለ የልጆች አስተዳደግ አበላል አለባበስ በሙሉ አኗኗር ማሳየት፡፡
3.ትውፊት
ትውፊት ማለት ቅብብል ርክክብ ውርርስ ማለት ነው፡፡
ይህም
-ቁሳዊ 
-ቃላዊ
-ሕይወታዊ ትውፊት አለ
-ቁሳዊ የምንለው መጻሕፍትን አድባራትን በሙሉ ንዋያትን ያካተተው ነው
-ቃላዊ የምንለው በቃል ሲተላለፍ የመጣው ያልተጻፈው ሁሉ ነው
-ሕይወታዊ የምንለው ኦርቶዶክሳዊ የሆነው እውነተኛ አኗኗር ነው፡፡
ወለህ ነቅዐ ሕይወት ጉባኤ ቤት በየዓመቱ በክረምት እየሰጠ ያለው ስልጣናም የዚህ አካል ነው ኦርቶክስን በትዳሩ በሥራው በኑሮዉ ሁሉ የሚገልፅ ሰው መፍጠር
መሪ ቃላችንም ንግበር ሰብአ (ሰው እንፍጠር) የሚል ነው፡፡
በዚህ ውይይት አሳብ በመስጠት ኦርቶዶክሳዊነትን በተግባር እናሳይ እላለሁ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 6593

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 5216

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 5305

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል...

    Read more: አብርሃም

  • 5197

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 4329

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form