ተወዳጆች እንደምን አላችሁ?
እንኳን አደረሳችሁ! 
ለምን አትሉም?
እሺ ለምን?
መጋቤ ምእመናን እና ወላዴ ሊቃውንት የሆነው የወለህ ነቅዐ ሕይወት ጉባኤ ቤት የልደት በዓል ነዋ!አሁን አራተኛ ዓመቱ ነው ይህ ጉባኤ ከተወለደ አራተኛ ዓመቱን እያከበረ ይገኛል በዚህ በልደቱ በዓልም የልደቴ እንዳትቀሩ ብሎ ከቤተ ክህነት ሠራተኛ እስከ መንግሥት ሠራተኛ እና መንፈሳውያን ማኅበራት ድረስ ለግለሰቦች ሳይቀር የጥሪ ደብዳቤ አድርሷል፡፡


በዚህም መሠረት ቀኑና ሰዓቱ ሲደርስ የተዘጋጀውን ጸበል ጸዲቅ ለማቅመስ በጸሎት ተባረከ ዳቦ ተቆርሶ ተሰጠ ቀጥሎም የጉባኤ ጸሎት ተደርጎ የመግቢያ መዝሙር ተዘመረ ቀጥሎም የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ተላለፈ በመልእክቱም ውስጥ ስንኳን የጉባኤ ቤት ልደት ይቅርና የአንድ ሰው እንኳን ልደት በደመቀ ሁኔታ ሲከበር እናያለን ይህማ ምንኛ አይደምቅ የሚል አሳብ አዘል ጉዳይ አለው! በማስቀጠልም መርሐ ግብሩ መሪው ለዕለቱ መምህር ዐውደ ምህረቱን ለቀቀ 
መምህሩ ማን ናቸው አትሉኝም?
እሺ መምህሩ ማን ናቸው?
ከባሕር ዳር ጀምሮ የመጡ የሐዲሳት የመነኮሳት የሊቃውንት መምሕር የሆኑት መምህር አስተርአየ ናቸዋ!
ምን አሉ?
የትምህርታቸው መነሻ ክቡር ዳዊት የተናገረው
" ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር -
ሀገረ እግዚአብሔር ሆይ ስለ አንቺ የሚነገረው ድንቅ ነው" መዝ 86.4 በማለት ጀምረው አንደኛ የኢየሩሳሌምን ድንቅ የሚያስብል ምሥጢር ዳሰሱ
ሁለተኛ  የእመቤታችንን አስደናቂ የድንግልናና የእናትነት ሕይወት የአምላክ እናት መሆንዋን አሰረግጠው ተናገሩ 
በሦስተኛ የቤተ ክርስቲያንን ልዩ ምሥጢር አሳይተው 
በአራተኛውና በመጨረሻው የጉባኤ ቤትን ድንቅነት እንዲህ ሲሉ አሳይታዋል 
እመቤታችን ግሩም እሳተ መለኮትን እንደተሸከመች ጉባኤ ቤትም ግሩም ቃለ እግዚአብሔር የሚመሠጠርባት የሊቃውንት መፍለቂያ ናት ይህም ድንቅ ነው፡፡
 እውነት ነው ጉባኤ ቤት ድንቅ ያልሆነች ማን ድንቅ ይሆናል?
በቃ ምን ልበላችሁ ድንቅ በሆነ አንደበት ድንቅ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡
በመቀጠልም ወረብ በመምህር ብርሃነ ሕይወት ተዘምሮ ቀጥታ ወደ ሪፖርት ተካሄደ ሪፖርቱን ያቀረቡት የጉባኤ ቤቱ ሊቀ ጉባኤ የሆኑት መምህር ዘመልአክ ዳግም ናቸው፡፡
 የቀረበውም በያዝነው ዓመት ምን ምን እንደተሠራና ምን ምን እንዳልተሠራ  ለታዳሚዎቹ የሚሳይ የተመጠነ ሪፖርት ነው፡፡ 
ቀጥሎ በመምህር ዕዝራ ቅኔ ቀረበ፡፡በመጨረሻ በነበረው መርሐ ግብር አስታያየትና ጥያቄ ከታዳሚዎች ተቀብሎ መርሐ ግብሩን በምሳ አጠናቀቀ፡፡
ስብሐት ለዘአብጽሐነ እምዝ
ከዚህ ለአደረሰን ምስጋና ይገባል
አብራችሁ እንደተሳተፋችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ 
ቸር ሁኑ! 

"የመምህራን መብዛት ለዓለም መድኃኒት ነው"
መምህር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት

Comments powered by CComment

ስብከቶች (Preaching)

  • 6593

    ሉቃስ ወንጌል ም። 18 ቁ። 1 __6

    1ሳይታክቱ ዘወትር  ሊጸልዩ  እንዲገባቸው የሚል ምሳሌ ነገራቸው፤ 2እንዲህ ሲል፤  “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። 3በዚያችው ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፤ ወደ እርሱም እየመጣች፣ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ’ ትለው ነበር።  4 አያሌ ቀንም አልወደደም ፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፤ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ፣ ሰውንም ባላፍር፣ 5ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ  እፈርድላታለሁ አለ።’  6ጌታም አለ፤ “ዓመፀኛው ዳኛ...

    Read more: ዘወትር ጸሎት

  • 5216

    ቀሲስ ሕብረት የሺጥላ፣ በስብከታቸው ከዚህ በታች ያሉትን እና ሌሎች ጥያቄዎችን ያብራራሉ፤ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (link ) በመጫን ስብከቱን ያድምጡ።

    1. የመላእክት አፈጣጠር
    2. የመላእክት ቁጥር ሰንት ነው?
    3. መላእክት ሰራቸው ምንድን ነው ?
    4. ማማለድ ምን ማለት ነው 

    Read more: መላእክት

  • 5305

    (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከነዚህ ነገሮች ቦኃላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው። እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፣ እንሆ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይሥሀቅን ይዘህ ወደሞርያም ምድር ኺድ እኔም በምነግርህ ባንድ ተራራ ላይ በዚያ ምሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ። አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፣ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሐቅን ከርሱ ጋር ወሰደ፣ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ ተነስቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።  (ኦሪት ዘፍጥረት ም.22  ቁ. 1.)

    ከዚህ ኃይለቃል...

    Read more: አብርሃም

  • 5197

    ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው። እርሱም መልሶ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው። ማቴዎስወንጌል ም. 4 ቁ - 1

    ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት ቀሲስ ሕብረት...

    Read more: ክርስቲያናዊ ጾም

  • 4329

    "እንሆ የእህትሽ የሰዶም ኀጢአት ይህ ነበረ። ትዕቢት ፣ እንጀራን መጥገብ ፣ መዝለልና ሥራ ምፍታት በርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበረ ፣ የችግረኛውንና የድሃውንም እጅ አላጸናችም። " ሕዝቃኤል 16 ቁጥር 42

    ቀሲስሕብረትየሺጥላ፣ ከዚህ ኃይለቃል በመነሳት፣በስብከታቸውከዚህበታችያሉትንእናሌሎችጥያቄዎችን...

    Read more: የሰዶም ኀጢአት

ማስታወቂያዎች

Login Form